Home

ወደ ዋና ገጻችን እንኳን በደህና መጡ!

Welcome to our church web site!

ካቴድራላችን ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ሲጠቀምበት የነበረውን መተዳደሪያ ደንብ በአዲስ ለመቀየር እና የሚቀጥሉትን ሰበካ ጉባኤ አባላት መርጦ ለማስረከብ እየሰራ ይገኛል። በዚህ ሂደት የካቴድራላችን አባላት ንቁ ተሳታፊ በመሆን በመተዳደሪያ ደንቡን በማጽደቅ ላደረጋችሁት ርብርብ ከፍተኛ ምስጋና እናቀርባለን።

ጠቅላላ ጉባኤው መጋቢት ፲፬ (March 23, 2025) በከፍተኛ ድምጽ (በአስር ድምጽ ተቃውሞ ብቻ) የቀድሞው መተዳደሪያ ደንብ በቀረበው አዲስ ድራፍት መተዳደሪያ ደንብ ረቂቅ ላይ አስተያየት ተካቶበት ለድምጸ ውሳኔ በአስቸኳይ እንዲቀርብ በወሰነው መሰረት የመተዳደሪያ ደንቡን ለማጽደቅ ልዩነት ባለባቸው ነጥቦች ላይ እሁድ መጋቢት ፳፰ (April 6, 2025) ፣ ሚያዚያ ፭ (April 13) ፣ ሚያዚያ ፲፱ (April 27) ለሦስት ሰንበቶች ድምጽ ተሰጥቶበት ድምጽ ከሰጡ 368 አባላት ከ95 በመቶ በላይ እንዲጸድቅ ወስኗል። በሚያዚያ 2017 (April 2025) ጸድቆ አገልግሎት ላይ ያለውን የካቴድራላችን መተዳደሪያ ደንብ ከዚህ በታች ያለውን መጠቆሚያ በመጫን ማግኘት እንደሚችሉ እናሳስባለን።

Click on the picture to download draft bylaw

 

Donate

ቤተ ክርስቲያናችን የመኪና መቆሚያ ማስፋፊያ እና ተጨማሪ ሦስት አሮጌ ቤቶች ያሉበት ግማሽ ኤከር መሬት በ2.9 ሚሊዮን ዶላር ገዝቶ በወር 15 ሺ ዶላር ሞርጌጅ እየከፈለ ሲሆን ቤቶቹን በፍጥነት አሳድሶ የልጆች ማስተማሪያ ሁለገብ አዳራሽ ለመገንባት ያስባል። ይህንን ጥረት ለማገዝ የሚችሉትን ሁሉ እንዲያደርጉ አደራ እንላለን።

ለቤተ ክርስቲያናችን አባላት እና ምዕመናን ለቤተ ክርስቲያን ስጦታ ፣ መባ ፣ አስራት ወይም ስለት ኦን ላይን መስጠት ከፈለጉ ከዚህ በታች ያለውን “ለቤተ ክርስቲያኑ ይለግሱ” የሚለውን ቁልፍ በመጫን ወደ ስኴር የመክፈያ በመሄድ የአቅሞትን መለገስ ይችላሉ።

About

Our Mission is :

To uphold the centuries-old tradition and values of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church; to increase the awareness of our community about the history, cultures, languages, and tradition of Ethiopia; and to provide other social services consistent with our religious practices.

News

ስልጠና ዛሬ ይጀምራል።

የተከበራችሁ የቤተ ክርስቲያናችን አባላት ዛሬ ምሽት ከ9PM ጀምሮ ክፍል ሁለት ስልጠና ይጀምራል። የዛሬው ስልጠና ቤተ ክርስቲያንን እወቅ በሚል ርዕስ አጠቃላይ መግቢያ ስለ ቤተ ክርስቲያን ሕግጋት ይሆናል። እንዳያመልጣችሁ። ለምትችሉት ሁሉ በቴክስት መልዕክት አጋሩ። https://zoom.us/j/97535530896?pwd=HM5JDaJZxa6nQx1U1QJorWAb97XNYC.1

Contact

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን
አድራሻችን

3010 Earl Pl NE,
Washington, DC 20018

ሳምንታዊ መርሃ ግብር
6:00 – 9:30 የኪዳንና ቅዳሴ ጸሎት
ከ9:30 – 11:00 ስብከተ ወንጌል
ከ12:00 – 1:30 ሰንበት ትምህርት ቤት መርሃ ግብር

የጥምቀት ፣ የተክሊል ፣ የፍትሐት ወዘተ አገልግሎት ማግኘት ከፈለጉ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ከ 9:00 – 4:00 በስልክ ቁጥር 202-529-7077 ይደውሉ።

 

የሕዝብ ግንኙነት ክፍልን ማግኘት ከፈለጋችሁ 240-308-8903 ይደውሉ።