እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን!!!!!

በደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ካቴድራል የጽርሐ ጽዮን ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሰን እንላለን!!!!

እንደሚታወቀው ሰንበት ትምህርት ቤታችን በዛሬው ዕለት በጌታ ትንሣኤ ከካህናት አባቶቻችንን ጋር የቆየ የምሳ መርሐ ግብር ልማድ ነበረን። ሆኖም ዓለምን ባስጨነቀው ወረርሺኝ ምክንያት እንደ ሌሎች የቤተ ክርስቲያን መርሐ ግብሮች እንደተለመደው ማካሄድ አልተቻለም። በመሆኑም እግዚአብሔር በምሕረቱ ጎብኝቶን ወደ ቀደመ ወደምንናፍቀው አገልግሎታችን እንዲመልሰን እየተማጸንን ይህቺን አጭር መልክእት በአባላቱ ስም እናስተላልፋለን።