የ25ተኛ ዓመት የሰበካ ጉባኤው (የቦርዱ) አስተዳደር መልዕክት

ከሁሉ አስ ቀድሜ ሃይማኖቱንና ሀገሩን ከማ ይረሳው ትውልድ ተቆጥረን የቤተ ክርስ ቲያናችንን ምሥረታ 25ኛ ዓመት ኢዮቤል ዩ መ ታሰቢያ በዓል
ለማክበር በመብቃታችን በራሴና ዛሬ እያገለገለ በሚገኘው የሰበካ ጉባኤ (ቦርድ) አስተዳደር ስም ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋናችንን አቀርባለሁ::
ካህናቱንና ሕዝቡን በፍቅርና በሕብረት ጠብቆ ለዚህ ታላቅ ቀን እንዳደረሰን ሁሉ እንዲሁ ባርኮና ጠብቆ ለ50ኛው ዓመት እንዲያደርሰን በጸሎት
በልመናና በምልጃ ተግተን እንደየተሰጠን ጸጋና መክሊት ለደብራችን አገልግሎት የተፋጠንን ሆነን እንድንቆይ አምላካችን ያበርታን::
በአሜሪካ ተወልደው ካደጉት በስተቀር እኛ አብዛኞቻችን በሥጋ ከተወለድንባት ሀገራችን በተለያዩ ምክንያቶችና ችግሮች ወጥተንና በፈቃድ
ለቀንም ስዱዳንና መጻተኞች ሆነን ባልተወለድንበት ሀገር ስንኖር ብዙ ዓመታት ተቆጥረዋል:: ሁላችንም ግን በቤተ ክርስቲያናችን ተገኝተንና
ተገናኝተን የኢትዮጵያ ልጆች ቅዳሴውን አስቀድሰን ዝማሬውን ሰምተንና ስብከተ ወንጌሉን ተመግበን በባዕድ አገር ስንኖር የክርስቶስ ቤተሰብነት
እንጂ ከቶውንም የመጻተኛነት ስሜት ኖሮን አያውቅም:: በየእሁዱ በየንግሡና በየክብረ በዓሉ ቁጥራችን እየበዛና ግንኙነታችን በመንፈሳዊና
በማኅበራዊ መስኮች እያደገ ሲሄድም የቤተ ክርስቲያናችን አገልግሎት አድጎና በልጽጎ በሰው ሀገር ያለን እስከማይመስለን ድረስ ትንሿን ኢትዮጵያ
የምናይበትና የምናገኝበት ዋና ሥፍራ ቤተ ክርስቲያን ሆኖ ቆይቶአል::
ለሁላችንም ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረተ ጀምሮ ለ25 ዓመታት ትንሿን ኢትዮጵያ አግኝተንበት በክርስቶስ አምነን፣
በትምህርተ ወንጌል ጸንተን፣ በነቢያትና በሐዋርያት ትምህርት ታንጸን የእግዚአብሔር ቤተሰብ ሆነን በክፉም በደጉም ተሳስረን ለነፍሳችንም
ለሥጋችንም ብዙ በረከት፣ ትሩፋትና ብልጽግና ያገኘንበት የተቀደሰ ሥፍራ ነው:: ቀናት ተቆጥረው ዘመን አዝማናት ተብለው የቤተ ክርስቲያናችን
ዕድሜ 25 ዓመት ሞላው ስንል ጊዜው እንዲህ መብረሩ በጣም ይገርማል:: እግዚአብሔር ፈቅዶና ባርኮ ቤተ ክርስቲያኑ ተመሥርቶ በሰጠው
አገልግሎት ብዙዎቻችን ተቀድሰንበታል፣ ተባርከንበታል፣ ተድረንበታል፣ ልጅ ወልደን፣ ክርስትና አስነስተን፣ በጋሪ ገፍተን አሳድገን፣ በአባቶች
ካህናት አቁርበን፣ በዘማርያን የዝማሬ ትምህርት አዘምረን፣ በሕፃናት ክፍል መምህራን ፊደል አስቆጥረን ልጆቻችን አማርኛ ማንበብና መጻፍ
ችለዋል:: በብዙው የተሳካላቸውም ወላጆች በደብሩ ትጉህና ምግባረ-ሠናይ ካህናት እውነተኛ ሐዋርያዊ ትጋት ግዕዝ ተምረው፣ ውዳሴ ማርያም
ደግመው፣ ለዲቁና በቅተው አንዳንዶቹም በቅዳሴ ጣዕመ ዜማቸው ከምድር እስከ አርያም መንፈሳዊ ልቡናችን እንዲያርግ እንዲጓዝ እያደረጉን
ነው::
የዲሲ ሰማይ ጠቀስ ፎቆች እንደአሁኑ ሳይገጠገጡና የዛሬው የቨራይዘን ሴንተር ሳይገነባ በዋሽንግተን ዲሲ በ8ተኛው ጎዳና በሰ ሜናዊው ምዕራብ
አቅጣጫ ከቀድሞው ስሚዞንያን ሙዚየም ትይዩ በኪራይ ቤዝመንት ውስጥ በቆሞስ አባ መልአኩ ጌታነህ የአሁኑ ብፁዕ አባታችን አባ ፋኑኤል
በቅዳሴያቸውና በትምህርተ ወንጌል ልዩ ችሎታቸው ሲያገለግሉ ነበር ብዙዎች ተስበን በደም ቅሚ ደብር የተገናኘነው:: ደብረ ም ሕረት ቅዱስ
ሚካኤል ደብሬ ብለን የአቅማችንን ገንዘብ እየሰጠንና ሳምንታቱን እየጠበቅን ወራትን እየቆጠርን ዓመታትን አስከትለን በፍቅርና በእውነተኛ
ክርስቶሳዊ ቤተሰብነት እያደግንና እየበዛን ተጉዘናል:: ጥብቅ ትሥሥራችንም በየጊዜው አርኪና ፍሬ-ብዙ ሆኖ በጥቂት ዓመታት የዛሬውን የደብሩን
ህንጻ በመግዛት እያደገ እየጨመረ ለመጣው የክርስቶስ ቤተሰብ፣ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጅና ተከታይ ሰፊ አገልግሎት መስጫ ቤተ ክርስቲያንና ርስት
በባዕድ አገር ሊኖረን ችሎአል::
ይህም ሥፍራ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሕንፃ ማሻሻያ ግንባታና የኢት ኦ/ቤ/ክ መልክ ይዞ እንዲታደስና እንዲሰራ እየተደረገ ሰፊ የመንፈሳዊ አገልግሎት
ከመስጠት አልፎ ለራሳችን ምዕመናንና ለሌሎችም የአካባቢው የእምነቱ ተከታዮች ለሠርግ፣ ለሃዘን፣ ለክርስትና፣ ለምርቃት (ግራጁዌሽን)፣
ለመንፈሳዊ ጉባኤዎችና ለሕፃናት ትምህርት አገልግሎት እየሰጠ ብዙ መንፈሳዊና ማህበራዊ ትሩፋትንና ጥቅሞችን አስገኝቶልናል::
በዚህ ረገድ የአባታችን የቆሞስ አባ መልአኩ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ችሎታ(የአሁኑ ብፁዕ አባታችን አቡነ ፋኑኤል) ለቤተ ክርስቲያኑ ፈጣን
ዕድገትና ከፍታ ቁልፍ ሚና ያላቸው ሲሆን የገንዘቡና የአገልግሎቱ ለጋሾችና ዋና ባለቤቶች የሆኑት ምዕመናን ወደር የሌለው ክርስቲያናዊ ፍቅር፣
እምነትና አንድነት ዘመን ተሻጋሪ የሆነ ከቅዱስ ሚካኤል ጋር የተሳሰረ የእምነትና የባለቤትነት መንፈስ ውጤትም ነው፡፡ በእነዚህ 25 ዓመታት ሁሉ
በተለያየ ደረጃና መጠን ነጻ ጊዜያቸውንና ዕውቀታቸውን ገንዘባቸውንም ጭምር እየሰጡ በቦርድ አባልነት ሲያገለግሉ የቆዩት ሁሉም ምዕመናን
ደከመን ሰለቸን ሳይሉ በአመራራቸውም በአገልግሎታቸውም ቤተ ክርስቲያኑን በየጊዜው እያደገና እየተስፋፋ እንዲሄድ ብቃት ያላቸውን መንፈሳዊ
አገልጋዮች በመቅጠር፣ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ሥራዎችን በሁሉም ረገድ ውጤታማ በማድረግ ለሰጡት አመራር ምስጋና ይገባቸዋል::
ከላይ የገለጽነው መልካም ሥራ ጋር በተለያዩ ምክንያቶች ደብሩ ፈተና ሲገጥመውም “ወዘሰ አዝለፈ ትዕግሥቶ ውእቱ ይድኅን -እስከ
6
የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል 25ኛ የብር ኢዮቤል ዩ
መጨረሻው የሚጸና እርሱ ይድናል” ማቴ 10፣22 በሚለው አምላካዊ ቃል መሠረት በጽናት ፣ በሽምግልና፣ በይቅርታና በህግ አግባብ የጋራ
መፍትሄ ላይ በማተኮር ካህናቱም ምዕመናኑም ሳይለያዩና ሳይበታተኑ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጅነትን አጠናክረው በመያዝ በጊዜ ሂደት ችግሮች
ተፈትተው ዕርቅ ሊወርድ ችሏል:: የሁሉም ወገን በሚስማማበት በመንፈሳዊ አገልግሎት የበላይነት ላይ ትኩረት በመደረጉም እግዚአብሔር ፈቅዶ
ዛሬ ከመቼውም በበለጠ ጊዜ የምእመናን የአንድነትና የሕብረት መንፈስ ሰርጾ ይገኛል::
ይህን የ25ኛ ዓመት ኢዮቤልዩ በዓል የምናከብረውም ባለንበት ሀገርና በቅድስት ሃገራችን ኢትዮጵያ የነበረው ሲኖዶሳዊ ክፍፍል ቀርቶ ወደ
አንድነት ከመጣን በኋላ በመሆኑ ሁላችንም ኦርቶዶክሳውያን እግዚአብሔር ይመስገን ብለን ደስታችንን እንገልጻለን:: በዚህ ረገድ ባለፈው ዓመት
ሐምሌ 16/2010 (ጁላይ 23/2018) የሲኖዶሱ አንድነት ዕርቅ ተካሄዶ ሲፈጸም ለዚህ ታሪካዊ አንድነት ማብሠሪያ ካቴድራላችን ተመርጦ ሐሙስ
ሐምሌ 19/ 2010 (ጁላይ 26/2018) የዕርቁና የአንድነቱ ዝርዝር መግለጫ ለመላው ዓለም ኢትዮጵያውያን የኦርቶዶክስ እምነት እምነት ተከታዮች
ይፋ ሲደረግ አባቶች ካህናትና ምእመናን በሰበካ ጉባኤያችን አስተባባሪነት በዕለቱ ይህን ታሪካዊ ታላቅ መርሐ ግብር ለማስተናገድ በመቻላችን
ዕድለኞችም ደስተኞችም ነበርን::ዛሬ እያገለገለ የሚገኘው የሰበካ ጉባኤ (ቦርድ) ያከናወናቸው ብዙ ተግባራትና ክንውኖች ቢኖሩም በወደፊቱ
የካቴድራላችን 25 ዓመታት ውስጥ ሊታዩና ሊከናወኑ ከሚገባቸው ነገሮች ውስጥ በቀረን የ2 ዓመት የአገልግሎት ዘመን ጊዜ እግዚአብሔር
ቢረዳን አሁን ካለን ይዞታና አገልግሎት ሻል ያለና ከፍ ያለ እርከን ገንብተን ለማለፍ በብርቱው የምንጥር ይሆናል:: ይህንንም ለጋሾቹና የአገልግሎት
ምንጫችን የሆኑትን ምዕመናን በመተማመን በጋራ በመሥራትና በፍጹም መንፈሳዊ ትሥሥራችን በመጓዝ የምናደርገው ይሆናል:፡ በዝርዝሩም
ሲገለጽ በአባቶች ካህናት፣ በወንድሞች ዲያቆናት፣ በደብሩ መዘም ራን፣ እንዲሁም የበጎ ፈቃድ ነጻ አገል ግሎት በሚሰጡ የል ዩ ልዩ ኮሚቴዎች
አባላትና በራሳቸው ተነሳሽነት ቤተ ክርስቲያንንና ምዕመናንን ከልባቸው ያለገደብ በሚያገለግሉ ወንድሞችና እህቶች ተሳትፎ በፍጹም ሃይማኖታዊ
ሥነ ምግባርና ዲሲፕሊን እንድንጓዝ ዕቅዶችና የተግባር መርሃ ግብሮችን እያወጣን እንሰራለን::
እግዚአብሔር አምላክ ላለፉት ዓመታት በሰላም በጤና ጠብቆ ለዚህ 25ኛ ዓመት መታሰቢያ ክብረ በዓል ስላደረሰን ስሙ የተመሰገነ ይሁን::
ሁላችንንም እንዲሁ በሰላም በጤና ጠብቆ ለሌላ 25ኛ ዓመት ያብቃን:: ሀገራችንን ኢትዮጵያንና ይህችንም የምንኖርባትን አሜሪካንን እግዚአብሔር
ይባርክ ይቀድስ እያልኩ በቤተ ክርስቲያናችን የሰበካ ጉባኤ (አስተዳደር ቦርድ) እና በራሴም ስም ለዚህ መጽሔት አንባቢያንና ለመላው የክርስቶስ
ቤተሰቦች ሁሉ እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ እያልኩ ልባዊ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ::