የ25 ተኛ ዓመት የሃገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ መልዕክት

ዘመናትን የምትለውጥ አንተ ግን ለዘለዓለሙ የማትለወጥ፣ ቀንና ሌሊትን፣ በጋንና ክረምትን የምታፈራርቅ ጌታ፣ ለደኅንነታችን የመረጥሃት
ዓመተምሕረት በቅዱስ ወንጌል ስ ላወጅክልን እናመሰግንሃለን።
እንኳን ለደብረ ም ሕረት ቅዱስ ሚ ካኤል ካቴድራ ል ሃያአምስተኛ ዓመት የም ሥረታ በዓል አደረሳችሁ።
ውድ ምዕመናን!
የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በዲሲና አካባቢው ለሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን ለሩብ ምዕተ ዓመት አንድም ቀን
የሚሰጠውን መንፈሳዊ አገልግሎት ሳያቋርጥ በሕያው እግዚአብሔር ቸርነት፣ በደገኛው በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት ከዛሬዋ ቀን የደረሰ
አንጋፋ ቤተክርስቲያን ነው።
ይህ ካቴድራል ባሳለፋቸው 25 ዓመታት ለነገይቱ ቤተክርስቲያን ተረካቢ የሆኑ ዲያቆናትን አስተምሮ ለግብረ ድቁና በማብቃት፣ለምዕመናንም
ቤተክርስቲያኒቷ የምትሰጠውን መንፈሳዊ አገልግሎቶች በሙሉ ማለትም ለሕፃናት ሥርዓተ ጥምቀትን በማከናወን፣በሥርዓተ ተክሊል በቁርባን
በማጋባት፣ ንስሐ በመስጠት ለቅዱስ ቁርባን በማቅረብ፣ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዪትንም በጸሎተ ፍትሐት በመሸኘት ከፍተኛ አገልግሎት የሰጠና፣
እየሰጠም የሚገኝ ቤተክርስቲያን ነው።
በይበልጥም በውጪው ዓለም አንድን ልጅ አስተምሮ ለግብረ ድቁና ማብቃት ብዙ ልፋትን የሚጠይቅና
ታላቅ አገልግሎት ሲሆን በዚህ አገልግሎት የደከሙና የሚደክሙትን ካህናት ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል።
የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በሀገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜ የሚፈጠሩ ችግሮ ችና ፈተናዎችን ጸሎ ትና ምህላ በመያዝ፣ እርዳታ
ለሚያስፈልጋቸው ገንዘብ አዋጥቶ በመርዳት፣ በተለይም የቤተክርስቲያን ዓይን የሆኑትን ገዳማትና መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ የሆኑትን የአብነት
ትምህርት ቤቶችን ድጋፍ በማድረግ ፣ በአሜሪካም ሆነ በሀገራችን ለሚገኙ ነዳያንን በማብላት ምግብና አልባሳት ቁሳቁሶችንም በማቅረብ
የኃይማኖት ግዴታዋን ስትወጣ ኖራለች።
[ ] እኔ በዚህ ቤተክርስቲያን በቁምስና ሳገለግል ከማልዘነጋቸው የእግዚአብሔር ቸርነቶች አንዱ እንደ ዛሬው በአካባቢውም ሆነ በሀገሩ ካህናት
ባልበዙበት ወቅት አንድም እሁድ እንኳን በሕመምም ሆነ በሌላ እክል የሰንበት አገልግሎቱ ተስጓጉሎ አያውቅም። ጉንፋን እንኳን ቢይዘኝ
እሁድን አሳልፎ በሚቀጥለው ቀን ሰኞ ነበር የሚያመኝ።ይህ የሰው ጥበብ ሳይሆን የእግዚአብሔር ሥራ የመልአኩም ተራዳይነት ስለነበር ዘወትር
በመገረምና በመደነቅ አምላኬን አመሰግን ነበር።
ዛሬ ይህ የደብረ ም ሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል
ጸጋው የበዛላቸው ብዙ አገልጋይ ካህናት፣ትጉኀን ምዕመናን ፣በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች አገልግሎቱን በስፋት እየሰጠ ይገኛል።
በተጨማሪም የዋሸንግተን ዲሲ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ሆኖ በማገልገልም ላይ ይገኛል።
ይህ ሁሉ በፍቅር መሠረትነት ተመስርቶ በፈቃደ እግዚአብሔር የበረከት ቦታ ለመሆን በቅቷል።ወደፊትም ከዚህ በላይ ብዙ ሥራዎች እንደሚሰራ
እናምናለን።
በመጨረሻም በባዕድ ሀገር በአንድም በሌላ ምክንያት አገናኝቶ ፣በተዋህዶ ጥላ በቤቱ ሰብስቦ፣ ዮሴፍን በስደት የረዳና ያበዛ እግዚአብሔር እኛንም
ረድቶን የቤተክርስቲያናችንን ምስረታ 25ኛ ዓመት ለማክበር በሕይወትና በጤና ስላደረሰን ልዑል አምላካችን እግዚአብሔር ክብር ምስጋና
ይግባው።
ለደብሩ ካህናት ፣ምዕመናን ረጅም እድሜና ጤና እየተመኘው፣የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የድንግል ማርያም አማላጅነት ፣ የመላእኩ የቅዱስ ሚካኤል
ጥበቃና ረድኤት አይለየን አሜን።
አባ ፋኑኤል
የዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ!